
ዓላማዎችና የጊዜ ዝርዝር
ይህ ዘርፈ ብዙ የጥናት መስክ በተለይም የአርኪኦሎጂ ፕሮጀክት በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ የላሊበላን አካባቢ (ላስታን) ስለ ተቆጣጠሩት የአማራ ህዝቦች ያለንን እውቀት የበለጠ ለማሳደግ ይፈልጋል፡፡
እኛ የአካባቢውን ማህበረሰብ ባህሉን ለመረዳትና ለማወቅ ፍላጎት አለን፡፡ ፕሮጀክቱ ስነ-ህይወታዊ፣ ማህበራዊ፣ ባህላዊና ቁሳዊ ትርጉምን በማብራራት በአገው ቋንቋ ተናጋሪዎችና ወደ አካባቢው በመጡት የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች መካከል የተደረጉትን የግንኙነት ውጤቶች የማብራራት አላማ አለው፡፡
ለዚህም ቁልፍ መለኪያዎችን በመመልከት ጥናት በምናደርግባቸው መዳረሻዎች (sites) የንጽጽር መረጃ ቋትን እየገነባን ነው፡፡ እነዚህም የመልክዓ-ምድር አጠቃቀም፣ ስነ-ህንጻ፣ የሸክላና ባህላዊ ቁሶች፣ የብረት ውጤቶች፣ የግድግዳ ስዕሎችና ሌሎች ልዩ ልዩ አይነት ገጽታዎች ያላቸው እንደ ዋሻ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ግድግዳዎችን ያስጌጡ የዝቅተኛ እርከኖች ቅርጾች ተስተውለዋል፡፡ ጎን ለጎንም የሚስተዋሉት የመካከለኛው ዘመን የግድግዳ ላይ ስዕሎችም በግልጽ ከንጉስ ይኩኖ አምላክ ጋር የተዛመዱ ናቸው፡፡
በአካባቢው የተገኙ የመካከለኛው ዘመን ሸክላዎችን በአይነታቸው በመመደብ (typology) በሌሎች የኢትዮጵያ መዳረሻዎች ላይ ከተገኙ ሸክላዎች ጋር ለማነጻጸር አቅደናል፡፡ ከንጉስ ይኩኖ አምላክ ጋር ተያያዥነት ያላቸው በእያንዳንዱ መዳረሻዎች ላይ የተገኙ የሰው ቅሪቶች በዛጔ ስረወ-መንግስት ከተሰራው ይምርሓነ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ካሉት አጽሞችና ሳይፈርሱ ከቆዩ አስከሬኖች ጋር ይነጻጸራሉ፡፡
ምንም እንኳ እኛ በአካባቢው ስላለው የመካከለኛው ዘመን ላይ ትኩረት ያደረግን ቢሆንም ከዚያ በፊት ስለነበረው ታሪክ ካልተጠቀሰ ግልጽ ሊሆን አይችልም፡፡
ስለዚህ እኛ በዋናነት ለምንፈልገው ጥናት ሊረዳን ስለሚችል ሁሉን አቀፍ ዘዴ በመጠቀም ሁሉንም ታሪካዊና ቅድመ-ታሪክ መረጃዎችን እንመረምራለን፡፡ ሁሉም የስራ ደረጃዎችና ጊዚያት ከግምት ውስጥ ተወስደው በትክክል ተመዝግበው ይተረጎማሉ፡፡ ለራሳችን ተዛማጅ ቁሳቁሶችን ማቅረብ ብቻ ሳይሆን በተጨማሪም ለወደፊት ለሚመጡ የአርኪኦሎጂ ስራዎች መረጃ ለመስጠት ነው፡፡
2001 ዓ.ም (2009 G.C)
የፕሮጀክቱ የመጀመርያ የመስክ ጉዞ የመሬት ገጽታ ላይ ያሉ ቁሶችን መሰብሰብ እና በርካታ መዳረሻዎችን በጥንቃቄ መመዝገብን ያካተተ ነበር፡፡ ለፕሮጀክቱ ስኬት ድጋፍቸውን ለማግኘት አንድ ወሳኝ ክፍል ከአካባቢው ማህበረሰቦች ጋር ተሳትፎ አድርጓል፡፡ በተጨማሪም ይህ ፕሮጀክት በቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን እንዲሁም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ፓትሪያሪክ ፍቃድን አግኝቷል፡፡
2002 ዓ.ም (2010 G.C)
የፕሮጀክቱ ዳይሬክተር በጤና ችግር ምክንያት መጓዝ ስላልቻለች ሁለት ኢትዮጵያዊ የቡድኑ አባላት አቶ ሃብታሙ ተስፋዬ እና አቶ አበበ መንግስቱ በ2001 ዓ.ም ያልተጎበኙ የጥናቱ መዳረሻዎች ላይ ተጨማሪ የመጀመርያ ደረጃ ጥናቶችን አድርገዋል፡፡ ስለሆነም እነዚህ ጥናቶች የፕሮጀክቱን ወሰን ለመግለጽ ይረዳሉ፡፡
2010 Tania Tribe's report for SOAS on her seed-corn funded research